By Abiy Wakuma
መጋቢነት ለሰዎች ነፍስ የመትጋት የተከበረ ጥሪ ነው፡፡ ለዋኖቻችሁ ታዘዙና ተገዙ፤ እነርሱ ስሌትን እንደሚሰጡ አድርገው፥ ይህንኑ በደስታ እንጂ በኃዘን እንዳያደርጉት፥ ይህ የማይጠቅማችሁ ነበርና፥ ስለ ነፍሳችሁ ይተጋሉ። ወደ ዕብራውያን 13፡7
መጋቢነት በእግዚአብሄር የሚሰጥ ፀጋ እንጂ በሰው አነሳሽነትና ፍላጎት የሚደረግ አገልግሎት አይደለም፡፡ ማንም ሰው ማንንም ስው ለመጋቢነት ሊጠራ አይችልም፡፡ ሰውም ራሱን ለመጋቢነት ሊያሰማራ አይችልም፡፡ የመጋቢነትን ፀጋ ሰጥቶ ሰውን ለመጋቢነት የአገልግሎት ስራ ሊጠራ የሚችለው እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እርሱም አንዳንዶቹ ሐዋርያት፥ ሌሎቹም ነቢያት፥ ሌሎቹም ወንጌልን ሰባኪዎች፥ ሌሎቹም እረኞችና አስተማሪዎች እንዲሆኑ ሰጠ፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡11
ሰው በአካባቢው ያለውን ክፍተት አይቶ መጋቢ መሆን አይችልም፡፡ ሰው ስለፈለገና ስለተመኘ ብቻ…
Read more
