• Home
  • About us
  • Albums
  • Blog

mezmur

  • Home
  • About us
  • Albums
  • Blog

ዘይት መሸጥ ችግሩ ምንድነው ? 

By Abiy Wakuma Dinsa

ኢየሱስን የምንከተል ሁላችን ከተባረክናባቸው በረከቶች አንዱ የስጋ ፈውስ ነው፡፡ እግዚአብሄር በክርስቶስ በኩል የሃጢያታችንን እዳ እንደከፈለና ነፍሳችን ከሃጢያት ነፃ እንዳወጣ ሁሉ እንዲሁ ኢየሱስ በመገረፉና ለስጋችን ፈውስና ጤንነት ሙሉ ዋጋ በመክፈሉ ፈውስ የእኛ ነው፡፡

ስለዚህ ነው የቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች በታመመ ሰው ላይ ዘይትት ቀብተው እንዲፀልዩለት መፅሃፍ ቅዱስ የሚያስተምረው፡፡

የቤተክርስትያን ሽማግሌዎች ሃላፊነት በቤተክርስትያናቸው ስለፈውስ ማስተማር ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስናስተምር የእግዚአብሄ ህዝብ እግዚአብሄር ለእርሱ ያለውን የፈውስ አላማ ሲረዳ ይፈወሳል፡፡ እምነት የእግዚአብሄርን ቃል ከመስማት ይመጣልና፡፡

እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 1017

የቤተክርስትያን ሽማግሌዎች በግልፅ እንደተፃፈው የእግዚአብሄር ቃል ትእዛዝ ለታመመ ሰው ዘይት ቀብተው መፀለይ ነው፡፡ ሽማግሌዎች በታመመ ላይ ዘይት ቀብተው በመፀለይ የእግዚአብሄርን ቃል መታዘዝ አለባቸው፡፡

ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። ያዕቆብ 5፡14

ያም ሆነ ይህ የእምነት ፀሎት ነው በሽተኛውን የሚፈውሰው፡፡ ሰው እግዚአብሄር ስለእርሱ ያለውን የፈውስ አላማ ከእግዚአብሄር ቃል ሰምቶ ሲያምን ይፈወሳል፡፡ ሐዋርያት 14፡9

ይህም ሰው ጳውሎስ ሲናገር ይሰማ ነበር፤ እርሱም ትኵር ብሎ ተመለከተውና ይድን ዘንድ እምነት እንዳለው ባየ ጊዜ፥

ሰወ የእግዚአብሄርን ቃል ሲሰማ እምነት ይኖረዋል፡፡ እምነት ሲኖረው እምነቱ ይፈውሰዋል፡፡

እርሱም፦ ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ አላት። ማርቆስ 5፡34

አንዳንድ አገልጋዮች ዘይት ቀብተው ለበሽተኞች ይፀልያሉ፡፡ ዘይቱን ወደቤቱ ወስፈዶ መፀለይ ለሚፈልግ ሰው ዘይትን ይሰጣሉ ወይም ይሸጣሉ፡፡ አንዳንድ ሰው ዘይቱን የሚገዛው መምጣት ላልቻለ ለታመመ ሰው ላይ ወስዶ ለመፀለይ ነው፡፡

ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ። ማቴዎስ 10፡8

ዘይቱን ስለመሸጥ ስናስብ የመሸጥ ችግሩ ምንድነው ዘይት ብለን እንደ እግዚአብሄር ቃል ማሰብ ይኖርብናል፡፡ ዘይት ገዝተው በሰው ላይ ለመቀባትና ለመፀለይ ወይም በራሳቸው ላይ ለመቀባትና ለመፀለይ ለሚፈልጉ ሰዎች ዘይቱን መሸጥ ችግሩ ምንድነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡

በደንብ ብናስበው ዘይቱ የሚገኘው በገንዘብ ነው፡፡ ትንሽም ቢሆን ማሸጊያና ሌሎች ወጭዎች ይኖሩታል፡፡ ያንን ወጪ ማን ይሸፍን ነው ጥያቄው? አገልጋዩ ያንን ወጭ ሸፍኖ በነፃ መስጠት ቢችል እሰየው ነው፡፡ ካልቻለ ግን ዘይቱን ለመግዛትና ለማሸግ ያወጣውን ወጭ ቢመልስ ችግሩ ምንድነው? ሰው በዘይቱ ከሚያገኘው መንፈሳዊ ጥቅም አንፃር የዘይቱን መጋና´ማሸጊያ ለጥቃቅን ወጪዎችን ቢከፍል ትልቅ ነገር ነውን?

እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆንን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን? 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡11

እውነት ነው ፀጋው ነፃ ነው፡፡ የፈውስ ስጦታው ነፃ ነው፡፡ ነገር ግን ዘይቱን ለመግዛትና ለማሸግ ነፃ አይደለም ገንዘብ ያስወጣል፡፡

በቅንነት ካየነው አገልጋዮች ለዘይቱና ለማሸጊያው ያወጡትን ተመጣጣኝ ዋጋ ቢመልሱ ምንም ችግር የለበትም፡፡

ይህ ማለት አገልጋዩ ስስታም አይሆንም ማለት አይደለም፡፡ ይህ ማለት አገልጋዩ በዚያ አጋጣሚ ተጠቅሞ ብዙ ገንዘብ ለማግኘት አይሞክርም እያልኩ አይደለም፡፡ አገልጋዩ ራስ ወዳድ ሊሆንና ከሰዎች መፈወስ በላይ የራሱን ጥቅም ሊያስቀድምና ካለምንም ምክኒያት ካወጣው ወጭ በላይ ብዙ እጥፍ ሊያስከፍል ይችላል፡፡ ይህ በፍፁም ተቀባይነት የሌለው ነገር ነው፡፡ ሰው ለዘይቱና ለማሸጊያው ያወጣውን ወጭ አስታኮ በነፃ የተቀበለውን የእግዚአብሄርን ነገር መሸጥ ስግብግብነት ነው፡፡

ኢየሱስን በግልፅ የተቃወመው መንፈሳዊ ነገርን ፈልገው የመጡ ሰዎችን ላይ አላግባብ መጠቀምን ነው፡፡

እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በጸሎት ርዝመት እያመካኛችሁ የመበለቶችን ቤት ስለምትበሉ፥ ወዮላችሁ፤ ስለዚህ የባሰ ፍርድ ትቀበላላችሁ። ማቴዎስ 23፡14

የእግዚአብሄርን ፈውስ ፈልገው የመጡን ሰዎች ይህን ያህል ገንዘብ ካልከፈላችሁ ብሎ የተጋነነ ገንዘብ መጠየቅና ማስጨነቅ ስጋዊነት ነው፡፡

በመጀመሪያይቱም ቤተክርስትያን መንፈስ ቅዱስን ለመሙላት ለሃዋሪያት ብር ሊሰጣቸው የሞከረውን ሰው ሃዋሪያት አጠንክረው ሲገስፁት እንመለከታለን፡፡ የእግዚአብሄርን ስጦታ በገንዘብ መቸርቸር በነፃ ተቀብላችሁዋልና በነፃ ስጡ የሚለው መፅሃፍ ቅዱሳዊ መርህ ይቃወማልና፡፡

ሲሞንም በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንዲሰጥ ባየ ጊዜ፥ ገንዘብ አመጣላቸውና። እጄን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ አለ። ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው፦ የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ። ሐዋርያት 8፡18-20

አገልጋዮች ስለኑሮዋቸው በእግዚአብሄርን መታመን አለባቸው፡፡ እግዚአብሄር የሰጣቸውን ነፃ ስጦታ በነፃ መስጠት አለባቸው፡፡ አገልጋዮች እግዚአብሄር የሰጣቸው ስጦታ ብዙ ገንዘብ ማግኛ መንገድ ለማድረግ ያለባቸውን ስጋዊ ፈተና ማሸነፍ እግዚአብሄን በስኬት እንዲየገለግሉት ያስችላቸዋል፡፡ አገልጋዮች የእግዚአብሄር ህዝብ መባረክ ፣ መጠቀምና መፈወስ ላይ ማተኮር አለባቸው፡፡ አገልጋዮች የእግዚአብሄርን መንግስትና ፅድቁን ሲፈልጉ እግዚአብሄር ደግሞ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ አንደሚያሟላላቸው በእግዚአብሄር መታመን አለባቸው፡፡

እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡ 31-33

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

08/10/2023

  • Leave a comment
  • Share
    ዘይት መሸጥ ችግሩ ምንድነው ?

    Share link

የስግደት አደጋው 

By Abiy Wakuma Dinsa

በእነዚህ ቀናት ከእግዚአብሄር ውጭ ለሰው ለመላእክት ለቅዱሳን ለሰማእታት ስግደት ይገባል አይገባም ስግደት ከተገባስ እስከምን ድረስ ነው ስግደት የሚገባው የሚለው ጥያቄ ሲያከራክር ቆይቶዋል፡፡

የዚህ ፅሁፍ አላማ የስግደትን አይነቶችና መጠን ለመተንተን ሳይሆን ከእግዚአብሔር ውጭ ያለ ስግደት ያለውን አደጋና ለምን ስግደት አደገኛ እንደሆነ ጥቂት ለማለት ነው፡፡

ስግደት ማለት እገዛልሃለሁ እታዘዝሃለሁ አንተ ጌታዬ ነህ ባንተ እታመናለሁ ማለት ነው፡፡ ስግደት ማለት አንተ ፈጣሪዬ ነህ እኔ ያንተ ነኝ ባንተ ተስፋ አደርጋለሁ ማለት ነው፡፡ ስግደት ማለት ለምንሰግድለት ነገር ራሳችንን አሳልፈን መስጠት ማለት ነው፡፡

በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ ስግደትን በተመለከተ ለእግዚአብሄር መስገድ እንደሚገባ በብዙ ቦታዎች ተጠቅሶዋል፡፡

ትኩረታችንን የሚፈልጉ እንድንሰግድላቸው በየጊዜው የሚፈትኑ የሚማርኩን ካልሰገድክልኝ ብለው የሚያስፈራሩ ብዙ ነገሮች በአለም ላይ አሉ፡፡ ጉልበት ሁሉ መንበርከክ ያለበት ግን ለእግዚአብሄር ነው፡፡

እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና። ሮሜ 14፡11

በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሄር ህዝብ ለእግዚአብሄር እንዲሰግዱ በብዙ ቦታዎች ታዞዋል፡፡ እግዚአብሄር ስለፈጠረን ስግደት እንደሚገባው መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡

ኑ፥ እንስገድ ለእርሱም እንገዛ፤ በእርሱ ባደረገን በእግዚአብሔር ፊት እንበርከክ፤ መዝሙር 95፡6

በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሄር ህዝብ ለእግዚአብሄር ብቻ እንጂ ለመልአክት እንዳይሰግዱ ታዞዋል፡፡

ልሰግድለትም በእግሩ ፊት ተደፋሁ። እርሱም፦ እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር የኢየሱስም ምስክር ካላቸው ከወንድሞችህ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ፤ የኢየሱስ ምስክር የትንቢት መንፈስ ነውና አለኝ። ራእይ 19፡10

በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሄር ህዝብ ለእግዚአብሄር ብቻ እንጂ እግዚአብሄርን ለሚመስል ነገር ስእል ወይም ምስል እንኳን እንዳይሰግዱ ታዞዋል፡፡

በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ። አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም፤ ዘፀአት 20፡4-5

ስግደት ለእግዚአብሄር ለአምላክነቱ ክብር የምናሳይበት መንገድ ነው፡፡ በመፅሃፍ ቅዱስ እግዚአብሄር ሊከበር እንደሚገባ በብዙ ቦታዎች ተጠቅሶዋል፡፡

ለእግዚአብሔር ክብርን ይስጡ፥ ምስጋናውንም በደሴቶች ይናገሩ። ኢሳያስ 42፡12

አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ለዘላለምም ስምህን አከብራለሁ፤ መዝሙር 86፡12

በመፅሃፍ ቅዱስ ከእግዚአብሄር በላይ ይሁን ከእግዚአብሄር እኩል ማንም እንዳይከበር በብዙ ቦታዎች ታዞዋል፡፡ እግዚአብሔር ከምንም ሰው ጋር ፣ ከማንም መላክእት ጋር ፣ ከየትኛውም ቅዱሳን ጋር አንደ አንዱ እንዲቆጠር አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር ታላቅ ነው፡፡

እግዚአብሔርን ከእኔ ጋር ታላቅ አድርጉት፥ በአንድነትም ስሙን ከፍ ከፍ እናድርግ። መዝሙር 34፡3

በመፅሃፍ ቅዱስ እግዚአብሄር ክብሩን ለማንም እንደማይሰጥ ተመልክቶዋል፡፡

እኔ እግዚአብሔር ነኝ ስሜ ይህ ነው፤ ክብሬን ለሌላ፥ ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም። ኢሳያስ 42፡8

በመፅሃፍ ቅዱስ እግዚአብሄር ክብሩን ለማንም ለስጋ ለባሽ እንደማይሰጥ ተመልክቶዋል፡፡

ለእግዚአብሔርም ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ። ሐዋሪያት 12፡23

በመፅሃፍ ቅዱስ እግዚአብሄር ክብሩን ለማንም መልአክ እንደማይሰጥ ተመልክቶዋል፡፡

እርሱም፦ እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር ከወንድሞችህም ከነቢያት ጋር የዚህንም መጽሐፍ ቃል ከሚጠብቁ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ አለኝ። ራእይ 22፡9

ሰይጣን የወደቀው እንደእግዚአብሄር መመለክ ስለፈለገ ነው፡፡ ሰይጣን የሚፈልገው መመለክንና እንዲሰገድለት ነው፡፡

ደግሞ ዲያብሎስ እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ ወሰደው፥ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም አሳይቶ፦ ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው። ማቴዎስ 4፡9

እግዚአብሄርን የሚያመልክና ለእርሱ የሚሰግድ ሰው ለሰይጣን አይሰግድም፡፡ ለእግዚአብሄር የማናመጣውን ማንኛውንም ስግደት የሚቀበለው ሰይጣን ነው፡፡ ለሰው ብንሰግድ ፣ ለመላእክት ብንሰግድ ፣ ለምስል ብንሰግድ ፣ ለዛፍም ብንሰግድ ፣ ለወንዝም ብንሰግድ ስግደቱን በተዘዋዋሪ የሚቀበለው ሰይጣን ነው፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር እንዲሰግድ ሰይጣን አይፈልግም፡፡

ሰው ለእግዚአብሄር አይስገድ እንጂ ለምንም ነገር ቢሰግድ ሰይጣን ደስ ይለዋል፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ካልሰገደ በተዘዋዋሪ ለእርሱ እንደሚሰግድ ሰይጣን ያውቃል፡፡

ዲያብሎስም፦ ይህ ሥልጣን ሁሉ ክብራቸውም ለእኔ ተሰጥቶአል ለምወደውም ለማንም እሰጠዋለሁና ለአንተ እሰጥሃለሁ፤ ስለዚህ አንተ በእኔ ፊት ብትሰግድ፥ ሁሉ ለአንተ ይሆናል አለው። ሉቃስ 4፡6-7

ትኩረታችሁ በእግዚአብሄር ላይ አይሁን እንጂ በምንም ነገር ላይ ቢሆን ሰይጣን ደስተኛ ነው፡፡ ትኩረታችሁ ከእግዚአብሄር ላይ ይነሳ እንጂ ትኩረታችንሁ ምንም ነገር ላይ ቢሆን ሰይጣን ተጠቃሚ ነው፡፡ ለእግዚአብሄር አትስገዱ እንጂ ለምንም ነገር ብትሰግዱ ሰይጣን ይጠቀማል፡፡ እግዚአብሄርን ብቻውን አትስገዱለት እንጂ ከምንም ነገር ጋር አብራችሁ ብትሰግዱለት ሰይጣን ግቡን ይመታል፡፡

የሰይጣን ግብ እግዚአብሄር ብቻውን እንዳይመልክ ነው፡፡ የሰይጣን ግብ እግዚአብሄር ከሌሎች ሰዎች ፣ ከሌሎች ቅዱሳን ፣ ከሌሎች መላእክት ጋር አብሮ እንደ አንዱ እንዲመለክ ነው፡፡ የሰይጣን ግንብ የእግዚአብሄርን ክብር በሰዎች ፣ በቅዱሳን ፣ በመላእክት ፣ በምስል መሸፈን ነው፡፡

እግዚአብሄር ደግሞ የሁሉም ፈጣሪ እና አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር እንደ አንዱ እንዲመለክ አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር ብቻውን መመለክ ነው የሚፈልገው፡፡ እግዚአብሄር ከምንም ከምንም ጋር እንዲቆጠር አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄርን ብቻውን ካላመለካችሁት ከማንም ጋር አብራችሁ እንድታመልኩት አይፈልግም፡፡

እኔ እግዚአብሔር ነኝ ስሜ ይህ ነው፤ ክብሬን ለሌላ፥ ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም። ኢሳያስ 42፡8

ስለዚህ ነው በአዲስ ኪዳን ለእግዚአብሄር የሚሰግዱ ሰዎች በተወሰነ ቦታ ሳይገደቡ በእውነትና በመንፈስ ባሉበት ቦታ ለእግዚአብሄር እንደሚሰግዱለት መፅሃፍ ቅዱስ የሚያስተምረው፡፡

ነገር ግን በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል አሁንም ሆኖአል፤ አብ ሊሰግዱለት እንደ እነዚህ ያሉትን ይሻልና፤ እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል። ዮሃንስ 4፡23-24

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

08/10/2023

  • Leave a comment
  • Share
    የስግደት አደጋው

    Share link

በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ ይመጣል 

By Abiy Wakuma Dinsa

አባቶቻችን በዚህ ተራራ ሰገዱ፤ እናንተም፦ ሰው ሊሰግድበት የሚገባው ስፍራ በኢየሩሳሌም ነው ትላላችሁ አለችው። ኢየሱስም እንዲህ አላት፦ አንቺ ሴት፥ እመኚኝ፥ በዚህ ተራራ ወይም በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ ይመጣል። እናንተስ ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ፤ እኛ መዳን ከአይሁድ ነውና ለምናውቀው እንሰግዳለን። ነገር ግን በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል አሁንም ሆኖአል፤ አብ ሊሰግዱለት እንደ እነዚህ ያሉትን ይሻልና፤ እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል። ዮሐንስ 4፡20-24

ኢየሱስ ከሳምራዊትዋ ሴት ጋር ሲነጋገር ለሁላችን ትልቅ መረዳትን የሚሰጥን ነገር ተናግሮዋል፡፡ ሳምራዊትዋ ሴት ሳምራዊያን በዚያ ተራራ ላይ ለእግዚአብሄር እንደሚሰገድ እንደሚያምኑ አይሁዳዊያን ደግሞ የሚሰገደው በኢየሪሳሌም ነው እንደሚሉና ተናገረች፡፡

ኢየሱ የመለሰላት መልስ ግን ከሁለቱም ለየት ያለ ነበር፡፡ ኢየሱስ በአዲሱ ኪዳን ሰው በዚያ ተራራም ይሁን በኢየሩሳሌም እግዚአብሄር እንደማይሰገድለት አስተማራል፡፡

እግዚአብሄር መንፈስ ነው፡፡ እግዚአብሄር በተራራ ላይ አይኖርም፡፡ እግዚአብሄር በኢየሩሳሌም አይኖርም፡፡ እግዚአብሄር በሁሉም ቦታ ይገኛል፡፡

ነገር ግን ነቢዩ፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠራላችሁ? ይላል ጌታ፥ ወይስ የማርፍበት ስፍራ ምንድር ነው? ይህንስ ሁሉ እጄ የሠራችው አይደለምን? እንዳለ፥ ልዑል የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም። ሃዋሪያት 7፡48-50

እግዚአብሄር ሰው በሰራው ቤተመቅደስ ውስጥ አይኖርም፡፡ እግዚአብሄርን  በሆነ ቤት ውስጥ ብንፈልገው አናገኘውም፡፡

ፈሪሳውያንም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤ ደግሞም፦ እንኋት በዚህ ወይም፦ እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው። ሉቃስ 17፡20

ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤ ሃዋሪያት 17፡24

እግዚአብሄር መንፈስ ነው፡፡ እግዚአብሄር በስጋ አይገኝም፡፡ እግዚአብሄ በአንድ አገር ውስጥ አይገኝም፡፡ እግዚአብሄር በአንድ ከተማ ውስጥ አይገኝም፡፡ እግዚአብሄር በአንድ ቤት ውስጥ አይገኝም፡፡ እግዚአብሄር በአንድ ስፍራ አይገኝም፡፡

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው? ኢሳያስ 66፡1

ለእግዚአብሄር የሚሰግዱለት ሰዎች በመንፈስ ሊያገኙት ይገባል፡፡ እግዚአብሄርን የሚያገኙት ሰዎች በመንፈስ ብቻ ሊያገኙት ይችላሉ፡፡ ለእግዚአብሄር የሚሰግዱለት ሰዎች በመንፈስ ብቻ ሊሰግዱለት ይችላሉ፡፡

እግዚአብሄር የሚፈልገው በስጋ የሚሰግዱለትን ሰዎች አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የሚፈልገው በመንፈስ የሚሰግዱለትን ሰዎች ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚፈልገው በእውነትና በመንፈስ የሚሰግዱለትን ሰዎች ነው፡፡ ለእግዚአብሄር በልባቸው የሚሰግዱለትን ሰዎች ይፈልጋል፡፡

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው? እነዚህን ሁሉ እጄ ሠርታለችና እነዚህ ሁሉ የእኔ ናቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን ወደዚህ ወደ ትሑት፥ መንፈሱም ወደ ተሰበረ፥ በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ። ኢሳያስ 66፡2

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

08/10/2023

  • Leave a comment
  • Share
    በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ ይመጣል

    Share link

ለጭንቀት ጥያቄ አምስቱ የተሳሳቱ መልሶች 

By Abiy Wakuma Dinsa

ሰይጣን ሰውን የሚያጠቃው በጭንቀት ነው፡፡ ሰይጣን ሃሳብን በመላክ ሰውን ያስጨንቃል፡፡ ሰይጣን ወደ ሰው አእምሮ ሃሳብን በመላክ ጥያቄዎችን ይጠይቃል፡፡

ሰይጣን እንደዚሁ አይነት ንግግር ጀምሮ ነው ሄዋንን የጣላት፡፡ ሰይጣን ሃሳብን ያስገባል፡፡ ሰይጣን ጥያቄዎችን ይጠይቃል፡፡

እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነበረ። ሴቲቱንም፦ በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት። ዘፍጥረት 3፡1

ሰይጣን ኢየሱስንም ሊጥለው የነበረው በተመሳይ መንገድ ነበር፡፡ ሰይጣን ጥያቄን ይጠይቃል፡፡ ለጥያቄው መልስ ከሌለን ሰይጣን ያስጨነቀናል፡፡ ለጥያቄው የተሳሳተ መልስ ከሰጠን እንጨነቃለን እንደክማለን ሰላማዊ ህይወታችን መኖር ያቅተናል፡፡

ፈታኝም ቀርቦ፦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። ማቴዎስ 4፡3

አሁንም ሰይጣን የሚዋጋን በዚሁ መልክ ነው፡፡ ሃሳብን ይልካል ፡፡ ሰይጣን ቅን ያልሆኑ ጥያቄዎችን ይጠይቃል፡፡ መልስ ካላገኘን ያስጨንቀለናል፡፡ ትክክለፃውን መልስ ካልሰጠን ያዋርደነባል፡፡

በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ። 2ኛ ቆሮንቶስ 11፡2-3

ሰይጣን ምንም ይበል ምንም ሰይጣን የተለያየ ርእስ ያምጣ የሰይጣን የጭንቀት ጥያቄ ሲጨመቅ እነዚህን የመሳሰሉ ናቸው፡፡

  1. አንተ አታውቅም

ሰይጣን አንተ አታውቅም የሚል እንደምታ ሊሰጠን ሲሞክር እኔ አውቃልሁ ብለን ከተንፈራገጥን ይጥለናል፡፡ አውቃለሁ ብለን ስላልተገለጠልን ወደፊት ማስረዳት ከሞከርን እንስታለን፡፡ ወይም ያልተገለጠልንን ወደፊት እኛ ራሳችን ፈልገን ለመድረስና ለመረዳትና ለማስረዳት ከሞከርን እንሳሳታለን፡፡ ሰይጣን አታውቅም ሲለን ራሳችንን ትሁት ማድረግ አለብን፡፡ የማናውቀውን አናውቅም ማለት ትህትና ነው፡፡ አዎ ስለ ወደፊቴ ሁሉንም ዝርዝር አላውቅም ማወቅም አያስፈልገኝም መልስ ነው፡፡ ሁሉን የሚያውቅ የሚመራኝ አባት አለኝ ማለት ይጠበቅብናል፡፡ ሁሉን የሚያውቀው ይጠነቀቅልኛል ይመራኛል፡፡

ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ኤርምያስ 29፡11

እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። 1ኛ ጴጥሮስ 5፡7

  1. አንተ አትችልም

ሌላው ሰይጣን የሚልከው የጭንቀት ጥያቄ ሲጨመቅ የምናገኘው ሌላው መልክት አንተ አትችልም የሚል ነው፡፡ እችላለሁ ብለን ከተከራከርነው የማንችልበትን ብዙ ተፈጥሮአዊ ምክኒያቶች ደርድሮ ያዳክመናል፡፡ አትችልም ለሚለው መልሱ አዎ በራሴ አልችልም የሚል ነው፡፡ አዎ በራሴ ጉልበት የለኝም ነገር ግን አንተን በመስቀል ላይ ድል የነሳህ ኢየሱስ ጉልበቴ ነው ማለት ይጠበቅብናል፡፡

ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ። ፊልጵስዩስ 4፡13

  1. ለእግዚአብሄር እየኖርክ አይደለም

ሌላው ከተቀበልነው ጭንቀት ውስጥ የሚያስገነባን ሰይጣን የሚልከው ሃሳብ ለጌታ እየኖርክ አይደለም የሚል ነው፡፡ ለዚህ መልሱ እግዚአብሄር በክርስቶስ ወዶኛል፡፡ ምንም ሳልሆነ ፣ ምንም ሳላደርግለትና ምንም ሳይኖረኝ ጠላት ሳለሁ ወዶኛል፡፡ እግዚአብሄር በክርስቶስ ደስ ተሰኝቶብኛል፡፡ እግዚአብሄር የማይፈልገው ነገር ካለ ደግሞ ይነግረኛል፡፡ አንተ የምን ቤት ነህ፡፡ አጥፍቼ ከሆነ ከእርሱ ጋር እጨርሳለሁ ፡፡ ይህ የቤተሰብ ጉዳይ ነው፡፡ በቤተሰብ ጉዳይ ጣልቃ አትግባ ማለት ይጠበቅብናል፡፡

  1. ይህ እና ያ የለህም

ሌላው ሰይጣንን የሚልከውን ሃሳብ እህ ብለን ከሰማነው ሊያሳምነን የሚሞከረው የሚያስፈልግህ የለህም የሚል ነው፡፡ ይህ እና ይህ ላይኖረኝ ይችላል፡፡ የሚያስፈክልገኝ ግን አለኝ፡፡ ይህ እና ይህ አሁን ላይኖረኝ ይችላል በሚያስፈልገኝ ሰአት ግን ይኖረኛል፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ የሌላኝ ግን የማያስፈልገኝነው፡፡ እግዚአብሄር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝ የለም፡፡ የሌለኝ ነገር ካለ አያስፈልገኝም ማለት ነው፡፡

እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። መዝሙር 23፡1

  1. ይህ ጉድለት አለብህ

አዎ ይህ ጉድለት አለብኝ፡፡ ስለዚህ ነው የእግዚአብሄ ፀጋ የተዘጋጀው፡፡ የማልችለውን ሊያስችል ጉድለቴን ሊሞላ ድካሜን ሊያበረታ ክፍተቴን ሊሸፍን የሚያስችል የእግዚአብሄር ፀጋ ተሰጥቶኛል፡፡

ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤ አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤ በብዙ መጽናት፥ በመከራ፥ በችግር፥ በጭንቀት፥ በመገረፍ፥ በወኅኒ፥ በሁከት፥ በድካም፥ እንቅልፍ በማጣት፥ በመጦም፥ በንጽህና፥ በእውቀት፥ በትዕግሥት፥ በቸርነት፥ በመንፈስ ቅዱስ፥ ግብዝነት በሌለው ፍቅር፥ በእውነት ቃል፥ 2ኛ ቆሮንቶስ 6፡4-6

እርሱም፦ ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ። 2ኛ ቆሮንቶስ 12፡9

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

08/10/2023

  • Leave a comment
  • Share
    ለጭንቀት ጥያቄ አምስቱ የተሳሳቱ መልሶች

    Share link

እግዚአብሔር የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን 

By Abiy Wakuma Dinsa

የገቢ ምንጫችሁ የሆነ ሰው ወደዳችሁም ጠላችሁም የወደፊት እድላችሁን ይወስናል፡፡ የገቢ ምንጫችሁን የሚያመጣ ሰው የሚለውን ላለመስማት ከባድ ብቻ ሳይሆን የማይቻልም ነው፡፡ ወደዳችሁም ጠላችሁም  የገቢ ምንጫችሁን የሚያመጣ ሰውን ራእይ በህይወታችሁ ታስፈፅማላችሁ፡፡

በገንዘብ ስለተገዙት ባሮች መፅሃፍ ቅዱስ የሚያስተምረው ይህንኑ ነው፡፡ ስለባሮች መፅሃፍ ቅዱስ ሲናገር እናንተ ክርስትያን ስለሆናችሁ የምታገለግሉትና የምትታዘዙት ጌታን ክርስቶስን ነው እንዲሁም የርስትን ብድራት የምትቀበሉት ከእርሱ ነው እያለ እግዚአብሄር ምንጫቸው መሆን እንዳለበት ያስተምራል፡፡ እግዚአብሄር ቀጣሪያቸውና ከፋያቸው ሲሆን በነፃነት ሰውን በማገልገል እግዚአብሄርን እንደሚያገለግሉ መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡

የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንደሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ። ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምትገዙ በትጋትና በበጎ ፈቃድ ተገዙ፤ ባሪያ ቢሆን ወይም ጨዋ ሰው፥ እያንዳንዱ የሚያደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ከጌታ በብድራት እንዲቀበለው ታውቃላችሁና። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡6-8

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ እግዚአብሄር ሲሆን ሰዎች እንዲያዩዋችሁ ለታይታ መኖርን ታቆማላችሁ፡፡

ሰዎች የገቢ ምንጫችሁ ሲሆኑ ከሰው እንጂ ከእግዚአብሄር የሚገኘውን ክብር ማግኘት አትፈልጉም፡፡ ሰዎች የገቢ ምንጫችሁ ሲሆኑ ከልባችሁ ሳይሆን ሰዎችን እያያችሁ ለታይታ ብቻ ትኖራላችሁ፡፡ ሰዎች የገቢ ምንጫችሁ ሲሆኑ ሰውን እንጂ እግዚአብሄርን ለማስደሰት አትፈልጉም፡፡

እናንተ እርስ በርሳችሁ ክብር የምትቀባበሉ ከአንዱም ከእግዚአብሔር ያለውን ክብር የማትፈልጉ፥ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ? የዮሐንስ ወንጌል 5፡44

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን ለጌታ ብቻ ለመኖር ነጻነትን ታገኛላችሁ፡፡

አገልጋይ ለኑሮ ገንዘብ ያስፈልገዋል፡፡ ቤተክርስትያን በምድር ላይ ተልእኮዋን ለመወጣት ገንዘብ ያስፈልጋታል፡፡ ለራእይ ማሳካት ገንዘብን እንዲሰጡ እግዚአብሄር ሰዎችን ይጠቀማል፡፡ ነገር ግን ሰዎች እግዚአብሄርን በመታዘዝ በገንዘባቸው ያገለግሉናል እንጂ የገቢ ምንጫችን በመሆን የሚፈልጉትን ነገር የሚያስደርጉን መሆን የለባቸውም፡፡ የገቢ ምንጫችን ሲሆን ብቻ ነውእግዚአብሄር የሰጠንን ነገር በገንዘቡ ሊገዛ የሚፈልግ ሰው ካለ እምቢ እንድንል አቅም የሚኖረን፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን እንደ ሀዋርያቱ  የእግዚአብሄርን ስጦታ በገንዘቡ ሊገዛ የሚመጣውን ሰው ከገንዘብህ ጋር ጥፋ ማለት እንችላለን፡፡

ሲሞንም በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንዲሰጥ ባየ ጊዜ፥ ገንዘብ አመጣላቸውና። እጄን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ አለ። ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው፦ የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ። የሐዋርያት ሥራ 8፡18-20

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን ማንም ሰው አያስፈራራችሁም

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን ማንም ሰው የእኔን ፍላጎት ካላሟላህ ገንዘብ መስጠትን አቆማለሁ ብሎ አያስፈራራችሁም፡፡ ሰው እናንተን በማገልገል እግዚአብሄርን እንደሚያገለግል ካልተሰማው ለእርሱም ለእናንተም አይጠቅምም፡፡ በገንዘቡ የሚያስፈራራችሁን ሰው በሰላም እንዲሄድ ትፈቅዱለታላችሁ፡፡ እግዚአብሄር ሰዎችን ሲጠቀም እግዚአብሄር በልባችን ያስቀመጠውን ራእይ እንድናደርግ እንጂ ገንዘብ የሚሰጡንን ሰዎች ራእይ እንድናደርግ አይደለም፡፡ በእነርሱ ውስጥ ያለውን ራእይ ማድረግ ከፈለጉ እኛ እናስፈልጋቸውም፡፡ እኛ  ከእግዚአብሄር የተቀበልነው በቂ ራእይ አለን፡፡ እግዚአብሄር የገቢ ምንጫችን ሲሆን ማንም ሰው እኔ የምፈልገውን ነግው የምታደርገው ካለበለዚያ ዋ ብሎ አያስፈራራንም፡፡

ሌሎች በእናንተ ላይ ይህን መብት የሚካፈሉ ከሆኑ እኛማ ይልቁን እንዴታ? ነገር ግን የክርስቶስን ወንጌል እንዳንከለክል በሁሉ እንታገሣለን እንጂ በዚህ መብት አልተጠቀምንም። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡12

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ማንም ሰው ክብራችሁን እንዲነካ አትፈቅዱለትም፡፡

ጌታ ምንጫችህ ሲሆን ማንም ሰው እኔ ባልሰጠው ይሞታል ብሎ ክብራችንን እንዲያዋርድ አንፈቅድለትም፡፡ ጌታ ምንጫችህ ሲሆን ማንም ሰው እኔ ባልደርስለት ዋጋ የለውም ነበር እንዲል አንፈቅድም፡፡ ለጌታ ልንሰጥና ልናገለግለውም ራሳችንን ሰጥተን የጌታን ስራ ለመስራት ሰውን አንለምንም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን የወንጌል ማህበርተኛ ለመሆን ሰዎችን በራሳችን ወጭ እናገለግላለን፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን በነፃ ወንጌልን የማገልገል ትምክታችንን ማንም ከንቱ እንዲያድርግብን አንፈቅድም፡፡

እኔ ግን ከእነዚህ ሁሉ ምንም አልተጠቀምሁም። እንዲህ እንዲሆንልኝ ይህን አልጽፍም፤ ማንም ትምክህቴን ከንቱ ከሚያደርግብኝ ሞት ይሻለኛልና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡15

እንግዲህ ደመወዜ ምንድር ነው? ወንጌልን እየሰበክሁ በወንጌል ካለኝ መብት በሙሉ እንዳልጠቀም ወንጌልን ያለ ዋጋ ብናገር ነው። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡18

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን በእኛ ማግኘት ጌታ ብቻውን ይመሰገናል፡፡

ጌታ ምንጫችን ሲሆን የጌታን ክብር ለማንም ስጋ ለባሽ እንሰጠም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን ማንንም ሰው እንደ አዳኛችን አናይም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን ለእኛ የሚሰጡ ሰዎች ለጌታ በመስጠታቸው እግዚአብሄርን ያመሰግናሉ እንጂ ራሳቸውን አያመሰግኑም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን ለእግዚአብሄር የሚሰጡ ሰዎች ለጌታ በመስጠታቸው ራሳቸውን እንደ እድለኛ ይቆጥራሉ፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን በህይወታችን የጌታና የሰው ክብር ከሚቀላቀል ሰዎች የሚያደረጉልን ጥቅም ቢቀርብን ይሻለናል፡፡

አብራምም የሰዶምን ንጉሥ አለው፦ ሰማይንና ምድርን ወደሚገዛ ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጄን ከፍ አድርጌአለሁ፤ አንተ፦ አብራምን ባለጠጋ አደረግሁት እንዳትል፥ ብላቴኖቹ ከበሉት በቀር ከእኔ ጋር ከሄዱትም ድርሻ በቀር፥ ፈትልም ቢሆን የጫማ ማዘቢያም ቢሆን፥ ለአንተ ከሆነው ሁሉ እንዳልወስድ አውናን ኤስኮልም መምሬም እነርሱ ድርሻቸውን ይውሰዱ። ኦሪት ዘፍጥረት 14፡22-24

ጌታ ምንጫችን ሲሆን በእናንት ማግኘት ማንም እንዲጠራ አትፈቅዱም

ጌታ ምንጫችን ሲሆን ለእኛ የሚሰጥ ሰው ለእግዚአብሄር እንደሰጠ መቁጠር አለበት፡፡ እንደው ለእኛ አዝኖ ብቻ የሚያድርግልንን አንቀበለም፡፡ እኛ ብዙዎችን ባለጠጋ የምናደርግ ሁሉ የእኛ የሆነ የእግዚአብሄር አገልጋዮች እንጂ የሚታዘንልን ምስኪን ሰዎች አይደለንም፡፡

ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡10

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን በሙሉ ልቡ ያልሆነ በስስት የሚሰጠውን ሰው አልቀበለም ማለት ትችላላችሁ

ጌታ ምንጫችን ሲሆን ብቻ ነው በደስታ ከሚሰጠው ሰው ብቻ የምንቀበለው፡፡ ደስ ሳይለው በልቡ እየሰሰተ የሚሰጥን ሰው ላለመቀበል ድፍረቱ የሚኖረን ጌታ ምንጫችን ሲሆን ብቻ ነው፡፡

የቀናተኛን ሰው እንጀራ አትብላ፥ ጣፋጩ መብልም አይመርህ፤ በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና፤ ብላ ጠጣ ይልሃል፥ ልቡ ግን ካንተ ጋር አይደለም። መጽሐፈ ምሳሌ 23፡6-7

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ለሰዎች ስለሚበዛው ስሌት እንጂ ስጦታቸውን ፈላጊ አትሆኑም

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ህይወታችሁን ይለውጣል ብለላችሁ ተስፋ የምታደርጉት አንድም ሰው ከሰማይ በታች አይኖርም፡፡ ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ሰዎች ለእግዚአብሄር ስራ ስለመስጠታቸው ለሰዎች ስለሚበዛው ስሌት እንጂ ስጦታቸውን ፈላጊ አትሆኑም፡፡

በስሌታችሁ የሚበዛውን ፍሬ እንጂ ስጦታውን ፈላጊ አይደለሁም። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4፡17

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን የእግዚአብሄርን ቃል በነፃነት ለመኖርና ለመስበክ ድፍረት ይኖተራችሁዋል፡፡ ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ለሰው ብላችሁ የእግዚአብሄርን ቃል እውነት አታመቻምቹም፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

08/10/2023

  • Leave a comment
  • Share
    እግዚአብሔር የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን

    Share link

እንደ እንጀራ ይሆኑልናል 

By Abiy Wakuma Dinsa

ለእስራኤልም ልጆች ማኅበር ሁሉ፦ ዞረን የሰለልናት ምድር እጅግ መልካም ናት። እግዚአብሔርስ ከወደደን ወተትና ማር ወደምታፈስሰው ወደዚች ምድር ያገባናል እርስዋንም ይሰጠናል። ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ አታምፁ፤ እንደ እንጀራ ይሆኑልናልና የምድሪቱን ሰዎች አትፍሩ፤ ጥላቸው ከላያቸው ተገፍፎአል፥ እግዚአብሔርም ከእኛ ጋር ነው፤ አትፍሩአቸው ብለው ተናገሩአቸው። ኦሪት ዘኍልቍ 14፡7-9

የእስራኤል ህዝብ ወደከንአን ሊገቡ ሲሉ ኢያሱ ምድሪቱን እንዲሰልሉ 12 ሰላዮችን ላከ፡፡ ከኢያሱና ከካሌብ በስተቀር ሁሉም ሰላዮች ስለምድሪቱ ክፉን ነገር ለእስራኤል ህዝብ አወሩ፡፡

ስለ ሰለሉአትም ምድር ክፉ ወሬ ለእስራኤል ልጆች እያወሩ፦ እኛ ዞረን የሰለልናት ምድር የሚኖሩባትን ሰዎች የምትበላ ምድር ናት፤ በእርስዋም ዘንድ ያየናቸው ሰዎች ሁሉ ረጃጅም ሰዎች ናቸው። ኦሪት ዘኍልቍ 14፡32

እነዚያ ሰላዮች እንዲያውም እኛ በእነርሱ ፊት እንደ አንበጣ ነን ብለው ራሳቸውን ዝቅ ዝቅ አደረጉ፡፡

በዚያም ከኔፊሊም ወገን የሆኑትን ኔፊሊም፥ የዔናቅን ልጆች፥ አየን፤ እኛም በዓይናችን ግምት እንደ አንበጣዎች ነበርን፥ ደግሞም እኛ በዓይናቸው ዘንድ እንዲሁ ነበርን አሉ። ኦሪት ዘኍልቍ 14፡33

እነዚህ አስሩ ሰላዮች ራሳቸውን እንጂ አብሮዋቸው የሚወጣውን የሰራዊት ጌታ ማየት አልቻሉ፡፡ ሊዋጉ የፈለጉት እንደዳዊት በእግዚአብሄር ስም ሳይሆን በራሳቸው ስም ነው፡፡

ዳዊትም ፍልስጥኤማዊውን አለው፦ አንተ ሰይፍና ጦር ጭሬም ይዘህ ትመጣብኛለህ፤ እኔ ግን ዛሬ በተገዳደርኸው በእስራኤል ጭፍሮች አምላክ ስም በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 17፡45

ዳዊት ሁልጊዜ የሚያስበው ጦርነቱን በየእለቱ የሚዋጋለት እግዚአብሄር ነው፡፡

አንድ ጊዜም እንዲህ ሆነ፡፡ በመጽሃፍ ቅዱስ የኤልሳ ባሪያ አንድ ጊዜ የጠላትን ሰራዊት ብዛት ተመልክቶ ልቡ ተሸበረ፡፡

የእግዚአብሔር ሰው ሎሌ ማለዳ ተነሥቶ በወጣ ጊዜ፥ እነሆ፥ በከተማይቱ ዙሪያ ጭፍራና ፈረሶች ሰረገሎችም ነበሩ። ሎሌውም፦ ጌታዬ ሆይ፥ ወዮ! ምን እናደርጋለን? አለው። መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 6፡15

ሲሸበር ኤልሳም እግዚአብሄር የብላቴናውን አይን እንዲከፍት ፀለየ፡፡

ኤልሳዕም፦ አቤቱ፥ ያይ ዘንድ ዓይኖቹን፥ እባክህ፥ ግለጥ ብሎ ጸለየ። እግዚአብሔርም የብላቴናውን ዓይኖች ገለጠ፥ አየም እነሆም፥ በኤልሳዕ ዙሪያ ያሉት የእሳት ፈረሶችና ሰረገሎች ተራራውን ሞልተውት ነበር። መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 6፡17

እርሱም፦ ከእኛ ጋር ያሉት ከእነርሱ ጋር ካሉት ይበልጣሉና አትፍራ አለው። መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 6፡16

አስሩ ሰላዮች ስለምድሪቱ ክፉ ወሬን አስወሩ፡፡ አስሩ ሰላዮች የጠላታቸውነ በዛት እነጂ የእግዚአብሄርን ትልቅነት አላስተዋሉም፡፡ አስሩ ሰላዮች የጠላታቸውን ሃያልነት እንጂ የእግዚአብሄርን ሃያልነት ረሱ፡፡

ሁለቱ ሰላዮች ግን የጠላታቸውን ብዛት ሳይክዱ የእግዚአብሄርን ታላቅነት ተመለከቱ፡፡

ስለዚህ እንዳውም ጠላት ሲበዛ ድል ይበዛል፡፡ እንደ እንጀራ ይሆኑልናል በማለት እግዚአብሄር ከእነርሱ ጋር ስላለ ምንም እንደማያቅታቸውና እነርሱን ማሸነፍ ለእግዚአብሄር ቀላል እንደሆነ ተናገሩ፡፡

ጠላት ሲገዝፍ ድላችን ይገዝፋል፡፡

ጨለማው በጨለመ መጠን ብርሃናችን ይደምቃል፡፡

ጠላት ሲተልቅ እንጀራው ይተልቃል፡፡

የጠላታችን ግዙፍነት የድላችንን መጠን ያገዝፈዋል፡፡

እኛ የምናሸንፈው ተሸናፊዎችን አይደለም፡፡ እኛ የምናሸንፈው አሸናፊዎችን ነው፡፡ እኛ የምናሸንፈው ብዙዎችን ያሸነፉትን ነው፡፡ እኛ የምናሸንፈው ብዙዎችን ያንበረከኩትን ነው፡፡ የአሸናፊዎች አሸናፊ ለመሆን አሸናፊውን ማሸነፍ ግዴታ ነው፡፡

በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፡37

ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ አታምፁ፤ እንደ እንጀራ ይሆኑልናልና የምድሪቱን ሰዎች አትፍሩ፤ ጥላቸው ከላያቸው ተገፍፎአል፥ እግዚአብሔርም ከእኛ ጋር ነው፤ አትፍሩአቸው ብለው ተናገሩአቸው። ኦሪት ዘኍልቍ 14፡7-9

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

08/10/2023

  • Leave a comment
  • Share
    እንደ እንጀራ ይሆኑልናል

    Share link

ስንሞት ምን እንሆናለን ? 

By Abiy Wakuma Dinsa

የገቢ ምንጫችሁ የሆነ ሰው ወደዳችሁም ጠላችሁም የወደፊት እድላችሁን ይወስናል፡፡ የገቢ ምንጫችሁን የሚያመጣ ሰው የሚለውን ላለመስማት ከባድ ብቻ ሳይሆን የማይቻልም ነው፡፡ ወደዳችሁም ጠላችሁም  የገቢ ምንጫችሁን የሚያመጣ ሰውን ራእይ በህይወታችሁ ታስፈፅማላችሁ፡፡

በገንዘብ ስለተገዙት ባሮች መፅሃፍ ቅዱስ የሚያስተምረው ይህንኑ ነው፡፡ ስለባሮች መፅሃፍ ቅዱስ ሲናገር እናንተ ክርስትያን ስለሆናችሁ የምታገለግሉትና የምትታዘዙት ጌታን ክርስቶስን ነው እንዲሁም የርስትን ብድራት የምትቀበሉት ከእርሱ ነው እያለ እግዚአብሄር ምንጫቸው መሆን እንዳለበት ያስተምራል፡፡ እግዚአብሄር ቀጣሪያቸውና ከፋያቸው ሲሆን በነፃነት ሰውን በማገልገል እግዚአብሄርን እንደሚያገለግሉ መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡

የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንደሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ። ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምትገዙ በትጋትና በበጎ ፈቃድ ተገዙ፤ ባሪያ ቢሆን ወይም ጨዋ ሰው፥ እያንዳንዱ የሚያደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ከጌታ በብድራት እንዲቀበለው ታውቃላችሁና። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡6-8

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ እግዚአብሄር ሲሆን ሰዎች እንዲያዩዋችሁ ለታይታ መኖርን ታቆማላችሁ፡፡

ሰዎች የገቢ ምንጫችሁ ሲሆኑ ከሰው እንጂ ከእግዚአብሄር የሚገኘውን ክብር ማግኘት አትፈልጉም፡፡ ሰዎች የገቢ ምንጫችሁ ሲሆኑ ከልባችሁ ሳይሆን ሰዎችን እያያችሁ ለታይታ ብቻ ትኖራላችሁ፡፡ ሰዎች የገቢ ምንጫችሁ ሲሆኑ ሰውን እንጂ እግዚአብሄርን ለማስደሰት አትፈልጉም፡፡

እናንተ እርስ በርሳችሁ ክብር የምትቀባበሉ ከአንዱም ከእግዚአብሔር ያለውን ክብር የማትፈልጉ፥ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ? የዮሐንስ ወንጌል 5፡44

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን ለጌታ ብቻ ለመኖር ነጻነትን ታገኛላችሁ፡፡

አገልጋይ ለኑሮ ገንዘብ ያስፈልገዋል፡፡ ቤተክርስትያን በምድር ላይ ተልእኮዋን ለመወጣት ገንዘብ ያስፈልጋታል፡፡ ለራእይ ማሳካት ገንዘብን እንዲሰጡ እግዚአብሄር ሰዎችን ይጠቀማል፡፡ ነገር ግን ሰዎች እግዚአብሄርን በመታዘዝ በገንዘባቸው ያገለግሉናል እንጂ የገቢ ምንጫችን በመሆን የሚፈልጉትን ነገር የሚያስደርጉን መሆን የለባቸውም፡፡ የገቢ ምንጫችን ሲሆን ብቻ ነውእግዚአብሄር የሰጠንን ነገር በገንዘቡ ሊገዛ የሚፈልግ ሰው ካለ እምቢ እንድንል አቅም የሚኖረን፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን እንደ ሀዋርያቱ  የእግዚአብሄርን ስጦታ በገንዘቡ ሊገዛ የሚመጣውን ሰው ከገንዘብህ ጋር ጥፋ ማለት እንችላለን፡፡

ሲሞንም በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንዲሰጥ ባየ ጊዜ፥ ገንዘብ አመጣላቸውና። እጄን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ አለ። ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው፦ የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ። የሐዋርያት ሥራ 8፡18-20

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን ማንም ሰው አያስፈራራችሁም

ጌታ የገቢ ምንጫችሁ ሲሆን ማንም ሰው የእኔን ፍላጎት ካላሟላህ ገንዘብ መስጠትን አቆማለሁ ብሎ አያስፈራራችሁም፡፡ ሰው እናንተን በማገልገል እግዚአብሄርን እንደሚያገለግል ካልተሰማው ለእርሱም ለእናንተም አይጠቅምም፡፡ በገንዘቡ የሚያስፈራራችሁን ሰው በሰላም እንዲሄድ ትፈቅዱለታላችሁ፡፡ እግዚአብሄር ሰዎችን ሲጠቀም እግዚአብሄር በልባችን ያስቀመጠውን ራእይ እንድናደርግ እንጂ ገንዘብ የሚሰጡንን ሰዎች ራእይ እንድናደርግ አይደለም፡፡ በእነርሱ ውስጥ ያለውን ራእይ ማድረግ ከፈለጉ እኛ እናስፈልጋቸውም፡፡ እኛ  ከእግዚአብሄር የተቀበልነው በቂ ራእይ አለን፡፡ እግዚአብሄር የገቢ ምንጫችን ሲሆን ማንም ሰው እኔ የምፈልገውን ነግው የምታደርገው ካለበለዚያ ዋ ብሎ አያስፈራራንም፡፡

ሌሎች በእናንተ ላይ ይህን መብት የሚካፈሉ ከሆኑ እኛማ ይልቁን እንዴታ? ነገር ግን የክርስቶስን ወንጌል እንዳንከለክል በሁሉ እንታገሣለን እንጂ በዚህ መብት አልተጠቀምንም። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡12

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ማንም ሰው ክብራችሁን እንዲነካ አትፈቅዱለትም፡፡

ጌታ ምንጫችህ ሲሆን ማንም ሰው እኔ ባልሰጠው ይሞታል ብሎ ክብራችንን እንዲያዋርድ አንፈቅድለትም፡፡ ጌታ ምንጫችህ ሲሆን ማንም ሰው እኔ ባልደርስለት ዋጋ የለውም ነበር እንዲል አንፈቅድም፡፡ ለጌታ ልንሰጥና ልናገለግለውም ራሳችንን ሰጥተን የጌታን ስራ ለመስራት ሰውን አንለምንም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን የወንጌል ማህበርተኛ ለመሆን ሰዎችን በራሳችን ወጭ እናገለግላለን፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን በነፃ ወንጌልን የማገልገል ትምክታችንን ማንም ከንቱ እንዲያድርግብን አንፈቅድም፡፡

እኔ ግን ከእነዚህ ሁሉ ምንም አልተጠቀምሁም። እንዲህ እንዲሆንልኝ ይህን አልጽፍም፤ ማንም ትምክህቴን ከንቱ ከሚያደርግብኝ ሞት ይሻለኛልና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡15

እንግዲህ ደመወዜ ምንድር ነው? ወንጌልን እየሰበክሁ በወንጌል ካለኝ መብት በሙሉ እንዳልጠቀም ወንጌልን ያለ ዋጋ ብናገር ነው። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡18

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን በእኛ ማግኘት ጌታ ብቻውን ይመሰገናል፡፡

ጌታ ምንጫችን ሲሆን የጌታን ክብር ለማንም ስጋ ለባሽ እንሰጠም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን ማንንም ሰው እንደ አዳኛችን አናይም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን ለእኛ የሚሰጡ ሰዎች ለጌታ በመስጠታቸው እግዚአብሄርን ያመሰግናሉ እንጂ ራሳቸውን አያመሰግኑም፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን ለእግዚአብሄር የሚሰጡ ሰዎች ለጌታ በመስጠታቸው ራሳቸውን እንደ እድለኛ ይቆጥራሉ፡፡ ጌታ ምንጫችን ሲሆን በህይወታችን የጌታና የሰው ክብር ከሚቀላቀል ሰዎች የሚያደረጉልን ጥቅም ቢቀርብን ይሻለናል፡፡

አብራምም የሰዶምን ንጉሥ አለው፦ ሰማይንና ምድርን ወደሚገዛ ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጄን ከፍ አድርጌአለሁ፤ አንተ፦ አብራምን ባለጠጋ አደረግሁት እንዳትል፥ ብላቴኖቹ ከበሉት በቀር ከእኔ ጋር ከሄዱትም ድርሻ በቀር፥ ፈትልም ቢሆን የጫማ ማዘቢያም ቢሆን፥ ለአንተ ከሆነው ሁሉ እንዳልወስድ አውናን ኤስኮልም መምሬም እነርሱ ድርሻቸውን ይውሰዱ። ኦሪት ዘፍጥረት 14፡22-24

ጌታ ምንጫችን ሲሆን በእናንት ማግኘት ማንም እንዲጠራ አትፈቅዱም

ጌታ ምንጫችን ሲሆን ለእኛ የሚሰጥ ሰው ለእግዚአብሄር እንደሰጠ መቁጠር አለበት፡፡ እንደው ለእኛ አዝኖ ብቻ የሚያድርግልንን አንቀበለም፡፡ እኛ ብዙዎችን ባለጠጋ የምናደርግ ሁሉ የእኛ የሆነ የእግዚአብሄር አገልጋዮች እንጂ የሚታዘንልን ምስኪን ሰዎች አይደለንም፡፡

ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡10

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን በሙሉ ልቡ ያልሆነ በስስት የሚሰጠውን ሰው አልቀበለም ማለት ትችላላችሁ

ጌታ ምንጫችን ሲሆን ብቻ ነው በደስታ ከሚሰጠው ሰው ብቻ የምንቀበለው፡፡ ደስ ሳይለው በልቡ እየሰሰተ የሚሰጥን ሰው ላለመቀበል ድፍረቱ የሚኖረን ጌታ ምንጫችን ሲሆን ብቻ ነው፡፡

የቀናተኛን ሰው እንጀራ አትብላ፥ ጣፋጩ መብልም አይመርህ፤ በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና፤ ብላ ጠጣ ይልሃል፥ ልቡ ግን ካንተ ጋር አይደለም። መጽሐፈ ምሳሌ 23፡6-7

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ለሰዎች ስለሚበዛው ስሌት እንጂ ስጦታቸውን ፈላጊ አትሆኑም

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ህይወታችሁን ይለውጣል ብለላችሁ ተስፋ የምታደርጉት አንድም ሰው ከሰማይ በታች አይኖርም፡፡ ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ሰዎች ለእግዚአብሄር ስራ ስለመስጠታቸው ለሰዎች ስለሚበዛው ስሌት እንጂ ስጦታቸውን ፈላጊ አትሆኑም፡፡

በስሌታችሁ የሚበዛውን ፍሬ እንጂ ስጦታውን ፈላጊ አይደለሁም። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4፡17

ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን የእግዚአብሄርን ቃል በነፃነት ለመኖርና ለመስበክ ድፍረት ይኖተራችሁዋል፡፡ ጌታ ምንጫችሁ ሲሆን ለሰው ብላችሁ የእግዚአብሄርን ቃል እውነት አታመቻምቹም፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

08/10/2023

  • Leave a comment
  • Share
    ስንሞት ምን እንሆናለን ?

    Share link

www.mezmur.com

All rights reserved 2023

Some images ©

  • Log out
Powered by Bandzoogle

notes
0:00/???
  1. 1
    የፀሎት ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ 1:20:44
    የፀሎት ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ

    Share link

    0:00/1:20:44
  2. 2
    የፅሞና ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ 1:08:16
    የፅሞና ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ

    Share link

    0:00/1:08:16
  3. 3
    የአምልኮ ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ 1:02:13
    የአምልኮ ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ

    Share link

    0:00/1:02:13
0:00/???