• Home
  • About us
  • Albums
  • Blog

mezmur

  • Home
  • About us
  • Albums
  • Blog
Back to all posts

ከመጠን በላይ የምንጓጓው ስለማናውቀው ነው

By Abiy Wakuma Dinsa

ው የአንድን ነገር ጥቅም ብቻ ሲያውቅ ያንን ነገር ለማግኘት በጣም ይጓጓል፡፡ በህይወታችን በጣም የምንጓጓለት ምንም ነገር ቢኖር እንረጋጋ፡፡ በህይወታችን በጣም የምንጓጓለት ምንም ነገር ቢኖር መጀመሪያ ይህ እንደዚህ የምጓጓለትን ነገር ሃላፊነትቱ በትክክል አውቀዋለሁ? ብለን ራሳችንን እንጠይቅ፡፡

በጣም የምጓጓለትን ነገር ሃላፊነቱን እስከምናውቅ ድረስ ማግኘታችን አደገኛ ነው፡፡ ጥቅሙን ብቻ እንጂ ሌላውን ጎኑን ሃላፊነቱን የማናውቅ ከሆነ አጠቃቀሙን እንደማናውቅ የኤሌክትሪክ ሃይል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ የሚያመዝን ሊሆንብን ይችላል፡፡ ሃላፊነቱን የማናውቀው ነገር በቀላሉ ያሰናክለናል፡፡

ዳሩ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እናገራለሁ፤ ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው ይሁኑ፥ የሚያለቅሱም እንደማያለቅሱ፥ ደስ የሚላቸውም ደስ እንደማይላቸው፥ የሚገዙም ምንም እንደሌላቸው፥ በዚችም ዓለም የሚጠቀሙ በሙሉ እንደማይጠቀሙባት ይሁኑ፤ የዚች ዓለም መልክ አላፊ ነውና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7፡29-31

ነገር ሁሉ ጊዜያዊ እንደሆነ አስብ፡፡ ነገ ልታዝን እንደማትችል አድርገህ ዛሬ ደስ አይበልህ፡፡ ነገ ደስታ እንደሌለ አድርገህ ዛሬ አትዘን፡፡

ደስታም የራሱ ሃላፊነት አለው፡፡ ሃዘንም የራሱ ሃላፊነት አለውከሃላፊነት ውጭ የሚመጣ ጥቅም የለም፡፡ እውነተኛ ጥቅም የሚመጣው ከሃላፊነት ጋር ነው፡፡

የተዋረደው ወንድም ግን በከፍታው፥ ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ፤ እንደ ሣር አበባ ያልፋልና። ፀሐይ ከትኵሳት ጋር ይወጣልና፥ ሣርንም ያጠወልጋልና፥ አበባውም ይረግፋልና፥ የመልኩም ውበት ይጠፋልና፤ እንዲሁ ደግሞ ባለ ጠጋው በመንገዱ ይዝላል። የያዕቆብ መልእክት 1፡9-11

ከመጠን በላይ የምንጓጓው ሃላፊነቱን ስለማናውቅ ነው፡፡ ከመጠን በላይ የምንጓጓው ጊዜያዊነቱን ስለማናውቅ ነው፡፡

ሰው የሆነ ነገር ስለማግኘቱ በጣም ሲፈነጥዝ ሲታይ ያስፈራል፡፡ ይህ ሰው ባገኘው ጥቅም እንደዚህ በጣም እንደፈነጠዘ ሁሉ በሃላፊነቱም እንደዚሁ ይሆን ይሆን ብሎ ያሳስባል፡፡

አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ . . . አገልግሎትህን ፈጽም። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:5

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ማድረግ ቢወዱ

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

02/02/2021

  • Leave a comment
  • Share
    ከመጠን በላይ የምንጓጓው ስለማናውቀው ነው

    Share link

Leave a comment

www.mezmur.com

All rights reserved 2023

Some images ©

  • Log out
Powered by Bandzoogle

notes
0:00/???
  1. 1
    የፀሎት ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ 1:20:44
    የፀሎት ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ

    Share link

    0:00/1:20:44
  2. 2
    የፅሞና ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ 1:08:16
    የፅሞና ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ

    Share link

    0:00/1:08:16
  3. 3
    የአምልኮ ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ 1:02:13
    የአምልኮ ጊዜ መዝሙሮች ስብስብ

    Share link

    0:00/1:02:13
0:00/???